Friday, August 26, 2011

ዲያቆን ዳን ኤል ክብረት የዓለም የሰላም አምባሳደ ተብሎ በፕሬዘዳንት ግርማ ተሸለመ

(ምንጭ፡-አዲስ ዘመን ነሐሴ 12 ቀን 2003ዓ.ም. 70ኛ ዓመት ቁጥር 342)

ቪዥን ኢትዮጵያ ፎረ ዲሞክራሲ የተባለ መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት መልካም ዜጋን በመቅረጽ እና የመልካም አስተዳደር ተግባራትን በማጠናከር ረገድ ከፍተኛ አስተዋጽኦ አድርገዋል ያላቸውን አራት ግለሰቦች ሊቀ ዲሞክራት እና ስድስት ግለሰቦችን ‘’የዓለም የሰላም አምባሳደር’’ የሚል ማዕረግ ሰጥቷል፣ በዚህም የነገረ ቤተክርስቲያን ተመራማሪ እና ደራሲ የሆነው ዲ/ን ዳንኤል ክብረት ‘’የዓለም የሰላም አምባሳደር’’ የሚል ማዕረግ ሰጥቶቷል፡፡


 
ስነስርዐቱ ላይ በመገኘት ማዕረጉን የሰጡት ፕሬዚዳንት ግርማ ወልደጊዮርጊስ ሲሆኑ የፌደራል ጉዳዮች ሚንስትር ዶ/ር ሽፈራው ተክለማርያም ‘’የዓለም የሰላም አምባሳደር’’ የሚል ማዕረግ ካገኙት ግለሰቦች አንዱ ናቸው፡፡ ቪዥን ኢትዮጵያ ፎረ ዲሞክራሲ ዋና ዳይሬክተር አቶ ታደለ ደርሰህ በስነስርዐቱ ላይ እንደገለጹት የተመረጡት ግለሰቦች በግልና በመንግስታዊ ተቋማት የላቀ ሥራ የሰሩ ናቸው፡፡ የዜጎች መብት እንዲታወቅ ና እንዲከበር ከፍ ያሉ ተግባራት አከናውነዋል አርአያና ምሳሌ ሆነው የሚጠቀሱም ናቸው ድርጅታችን ወደፊትም እንዲህ ያሉ ግለሰቦችንና ኃላፊዎችን ለተግባራቸው ዕውቅና በመስጠት የመሸለም ሥራ እንደሚሰራ ገልጸዋል፡፡ ለአገልግሎት ባሕር ማዶ የሚገኘው ዲ/ን ዳንኤል ክብረትም በባለቤቱ አማካኝነት የማዕረግ ስጦታውን ተቀብሏል

No comments:

Post a Comment