Tuesday, August 30, 2011

መምህር ግርማ ታገዱ

  • ድቁና እንጂ ቅስና የለኝም በማለታቸው ታግደዋል - ሊቀጳጳስ አባ ቆውስጦስ
  • ማስረጃ በማቅረቤ እግዱ ተነስቶልኛል - መምህር ግርማ
  • በድቁና የሚያገለግል ሰው ይላላካል እንጂ አያጠምቅም
  • እኔ ቅስናዬን ደብቄ ነው

ከስርዓት ውጭ በአዲስ አበባና በክልል ከተሞች በርካታ ሰዎችን ፀበል አጠምቃለሁ እያሉ ከአንድ ሚሊዮን ብር በላይ የሚያወጣ ቤት ገዝተዋል የሚል ቅሬታ የቀረበባቸው መምህር ግርማ ወንድሙ፤ የ1.5 ሚ. ብር መኖሪያ ቤትና ፒክአፕ መኪና ያገኘሁት በስጦታ ተገዝቶልኝ ነው ብለዋል - መምህር ግርማ”
ቪሲዲ፣ ጋዜጣና መጽሔት ምር የመምህር ግርማ ነው እየተባለ በየቤተክርስትያኑ ሲሸጥ አይተናል የሚሉ ቅሬታ አቅራቢዎች፤ በቤተክርስትያን ብቻ ሳይሆን በቤታቸውም ፀበል አጠምቃለሁ እያሉ ከምዕመናን ብር ይሰበስባሉ በማለት ይተቻሉ፡፡ ከስርዓት ውጭ በሆነ መንገድ በሚሰበስቡት ብር፤ የ1.5 ሚ.ብር ቤት፤ ፒክአፕ መኪና፤ ሚኒባሶችና ሌሎች ንብረቶችን አካብተዋል ይላሉ - ቅሬታ አቅራቢዎች፡፡

በደቡብ ወሎ ሀገረ ስብከት 12 የሰንበት ት/ቤቶች ባቀረቡት ቅሬታ፣ መምህር ግርማ የሚያካሂዱት የማጥመቅ ስራ ስርዓት የጣሰ ስለሆነ ሊያቆሙ ይገባል ብለዋል፡፡ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የብፁዕ ወቅዱስ ፓትሪያርክ ረዳትና የሰሜን ሸዋ ሰላሌ ሀ/ስብከት ሊቀ ጳጳስ አባ ቆውስጦስ፤ መምህር ግርማ ላይ እገዳ የተጣለው ቅስና የሌለው ሰው ማጥመቅ ስለማይችል ነው ብለዋል፡፡ በድቁና የሚያገለግል ሰው ይላላካል እንጂ አያጠምቅም  የሚሉት አባ ቆውስጦስ፤ በአቶ ግርማ ላይ ቅሬታ ስለቀረበ ጠርተን ስናናግራቸው፤ ድቁና እንጂ ቅስና የለኝም  በማለታቸው ሊታገዱ ችለዋል ብለዋል፡፡

መምህር ግርማ በበኩላቸው እኔ ቅስናዬን ደብቄ ነው እንደዚያ ያልኩት ሲሉ ምላሽ ሰጥተዋል፡፡ ጥያቄ የቀረበልኝ በቁጣ በመሆኑ ቅስና የለኝም ብዬ ተናግሬያለሁ የሚሉት መምህር ግርማ፤ አሁን ማስረጃ በማቅረቤ እግዱ ተነስቶልኛል ይላሉ፡፡ አቡነ ቆውስጦስ ግን እግዱ አልተነሳም ብለዋል፡፡ አቶ ግርማ እግዱ ከተወሰነባቸው በኋላ ቅስና ስላለኝ እግዴ ይነሳልኝ የሚል ጥያቄ አቅርበው ነበር የሚሉት አቡነ ቀውስጦስ፤ እኛ ሀሜትና ወሬን በመከተል ሳይሆን፤ በህጋዊ መንገድ ጠይቀን የደረስንበት ውሳኔ ነው ብለዋል፡፡

 በመምህር ግርማ ንብረት ላይ ስለሚሰነዘረው ቅሬታ ተጠይቀው፤ ስለሌላው ጉዳያቸው እኛ አያገባንም ብለዋል አቡነ ቀውስጦስ፡፡ መምህር ግርማ በበኩላቸው፤ ከዚህ በፊትም መተተኛ ነው፣ አስማተኛ ነው የሚል አሉባልታ እየተወራብኝ ነበር፤ ያ አልሳካ ሲላቸው ቅስና የለውም ተብያለሁ ይላሉ፡፡ አሁንም በሥራ ላይ መሆናቸውን በመጥቀስ ማንም በአሉባልታ ከምወደው ምዕመን አይለየኝም የሚሉት መምህር ግርማ፤ንብረታቸውን በተመለከተ በሰጡት መልስ የውጪ ተመራማሪና የጆርጅ ቡሽ አማካሪ የነበሩ ግለሰብ ሲፈወሱ በ1.5 ሚሊዮን ብር ቤትና ፒካፕ መኪና ተገዛልኝ፤ ይሔ ስጦታዬ ነው፤ ወሬኞች ግን ካቻማሊና ሚኒባስ አለው ብለው ያስወራሉ ብለዋል፡፡

"ማለዳም። ሰማዩ ደምኖ ቀልቶአልና ዛሬ ይዘንባል ትላላችሁ። የሰማዩን ፊትማ መለየት ታውቃላችሁ፥ የዘመኑንስ ምልክት መለየት አትችሉምን?"- ማቴ 16:3 

‹‹ሐሰት አንናገርም፤ እውነትንም አንደብቅም››
From Addis Admas

No comments:

Post a Comment