Tuesday, August 30, 2011

መምህር ግርማ ታገዱ

  • ድቁና እንጂ ቅስና የለኝም በማለታቸው ታግደዋል - ሊቀጳጳስ አባ ቆውስጦስ
  • ማስረጃ በማቅረቤ እግዱ ተነስቶልኛል - መምህር ግርማ
  • በድቁና የሚያገለግል ሰው ይላላካል እንጂ አያጠምቅም
  • እኔ ቅስናዬን ደብቄ ነው

ከስርዓት ውጭ በአዲስ አበባና በክልል ከተሞች በርካታ ሰዎችን ፀበል አጠምቃለሁ እያሉ ከአንድ ሚሊዮን ብር በላይ የሚያወጣ ቤት ገዝተዋል የሚል ቅሬታ የቀረበባቸው መምህር ግርማ ወንድሙ፤ የ1.5 ሚ. ብር መኖሪያ ቤትና ፒክአፕ መኪና ያገኘሁት በስጦታ ተገዝቶልኝ ነው ብለዋል - መምህር ግርማ”
ቪሲዲ፣ ጋዜጣና መጽሔት ምር የመምህር ግርማ ነው እየተባለ በየቤተክርስትያኑ ሲሸጥ አይተናል የሚሉ ቅሬታ አቅራቢዎች፤ በቤተክርስትያን ብቻ ሳይሆን በቤታቸውም ፀበል አጠምቃለሁ እያሉ ከምዕመናን ብር ይሰበስባሉ በማለት ይተቻሉ፡፡ ከስርዓት ውጭ በሆነ መንገድ በሚሰበስቡት ብር፤ የ1.5 ሚ.ብር ቤት፤ ፒክአፕ መኪና፤ ሚኒባሶችና ሌሎች ንብረቶችን አካብተዋል ይላሉ - ቅሬታ አቅራቢዎች፡፡

በደቡብ ወሎ ሀገረ ስብከት 12 የሰንበት ት/ቤቶች ባቀረቡት ቅሬታ፣ መምህር ግርማ የሚያካሂዱት የማጥመቅ ስራ ስርዓት የጣሰ ስለሆነ ሊያቆሙ ይገባል ብለዋል፡፡ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የብፁዕ ወቅዱስ ፓትሪያርክ ረዳትና የሰሜን ሸዋ ሰላሌ ሀ/ስብከት ሊቀ ጳጳስ አባ ቆውስጦስ፤ መምህር ግርማ ላይ እገዳ የተጣለው ቅስና የሌለው ሰው ማጥመቅ ስለማይችል ነው ብለዋል፡፡ በድቁና የሚያገለግል ሰው ይላላካል እንጂ አያጠምቅም  የሚሉት አባ ቆውስጦስ፤ በአቶ ግርማ ላይ ቅሬታ ስለቀረበ ጠርተን ስናናግራቸው፤ ድቁና እንጂ ቅስና የለኝም  በማለታቸው ሊታገዱ ችለዋል ብለዋል፡፡

መምህር ግርማ በበኩላቸው እኔ ቅስናዬን ደብቄ ነው እንደዚያ ያልኩት ሲሉ ምላሽ ሰጥተዋል፡፡ ጥያቄ የቀረበልኝ በቁጣ በመሆኑ ቅስና የለኝም ብዬ ተናግሬያለሁ የሚሉት መምህር ግርማ፤ አሁን ማስረጃ በማቅረቤ እግዱ ተነስቶልኛል ይላሉ፡፡ አቡነ ቆውስጦስ ግን እግዱ አልተነሳም ብለዋል፡፡ አቶ ግርማ እግዱ ከተወሰነባቸው በኋላ ቅስና ስላለኝ እግዴ ይነሳልኝ የሚል ጥያቄ አቅርበው ነበር የሚሉት አቡነ ቀውስጦስ፤ እኛ ሀሜትና ወሬን በመከተል ሳይሆን፤ በህጋዊ መንገድ ጠይቀን የደረስንበት ውሳኔ ነው ብለዋል፡፡

 በመምህር ግርማ ንብረት ላይ ስለሚሰነዘረው ቅሬታ ተጠይቀው፤ ስለሌላው ጉዳያቸው እኛ አያገባንም ብለዋል አቡነ ቀውስጦስ፡፡ መምህር ግርማ በበኩላቸው፤ ከዚህ በፊትም መተተኛ ነው፣ አስማተኛ ነው የሚል አሉባልታ እየተወራብኝ ነበር፤ ያ አልሳካ ሲላቸው ቅስና የለውም ተብያለሁ ይላሉ፡፡ አሁንም በሥራ ላይ መሆናቸውን በመጥቀስ ማንም በአሉባልታ ከምወደው ምዕመን አይለየኝም የሚሉት መምህር ግርማ፤ንብረታቸውን በተመለከተ በሰጡት መልስ የውጪ ተመራማሪና የጆርጅ ቡሽ አማካሪ የነበሩ ግለሰብ ሲፈወሱ በ1.5 ሚሊዮን ብር ቤትና ፒካፕ መኪና ተገዛልኝ፤ ይሔ ስጦታዬ ነው፤ ወሬኞች ግን ካቻማሊና ሚኒባስ አለው ብለው ያስወራሉ ብለዋል፡፡

"ማለዳም። ሰማዩ ደምኖ ቀልቶአልና ዛሬ ይዘንባል ትላላችሁ። የሰማዩን ፊትማ መለየት ታውቃላችሁ፥ የዘመኑንስ ምልክት መለየት አትችሉምን?"- ማቴ 16:3 

‹‹ሐሰት አንናገርም፤ እውነትንም አንደብቅም››
From Addis Admas

‹‹ ፋሽስት ጣልያን አሽቀንጥሮ የጣለልንን ቀንበር መልሰን አንሸከምም ››መምህር ተስፋዬ ሸዋዬ



  • ስልጣነ ክህነት የሚያላብስ ሊቀጳጳስ አሁንም በመንበር ላይ የለም 
  • ፋሽስት ጣልያን አሽቀንጥሮ የጣለልንን ቀንበር መልሰን አንሸከምም 
  • …..በ 1974 ዓ.ም ዶክተሮቹ ጳጳሳት ደካማውን ፓትርያልክ አንከርፍፈው ሮም ወስደው ለፓፓው አሰግደው…….‹‹ ውይ እዚህው ድረስ እንዲያው ደከማችሁ እዛው ካርዲናል ሾሜላችሁ የለም እንዴ እዚያው በማሰልጠን ትምህርት አመሳስሉ›› ተብለው መመሪያ ተቀበሉ 
  • የቤተክርስትያን ሐብቷ ሰው እንጂ ገንዘብ አይደለም 
  • አሁን በቤተክርስትያን ቁንጮ ላይ ሆነው የሚራኮቱት በአሜሪካ በራሽያ በሩማንያ የተማሩ እርስ በርሳቸው የሚናናቁ ናቸው 
  • የተዋህዶ ሐይማኖታችን እምነትና ትምህርት አይለወጥብንም ስርዓታችን አይናወጥብንም መቅደሳችን አይደፈርብንም የሚለው እንቅስቃሴ ለራስ ገፅታ ግንባታ ለማዋል መራወጥ ይታያል፡፡ 
  • ይህ ሁኔታ እንዳይከሰት 1600 ዓ.ም በተጠንቀቅሰ ሲጠብቁ ኖረዋል አሁን ግን የተባለው ሊፈፀም ግድ ስለሆነ የማይቀር ነውና ምዕመኑ ሊሸበር አይገባም 
    ሊቅነት መንፈሳዊነት ነው ብለው ያምናሉ 
    ሊቅነት ከመንፈሳዊነት ጋር ግንኙነት የለውም ፡፡ መንፈሳዊነት ፤ ትህትና ፤ ትዕግስትን ፤ ፍቅርን ፤ ርህራሄን፤  ደስታን ፤ ሰላምን ፤ የመንፈስ ፍሬዎች የተባሉትን ሁሉ የተላበሰ መሆን ነው፡፡ ሊቅነት ግን የዚህ ተቃራኒ ነው
  • ....ባንድ በኩል በተለያዩ ፓርቲዎች ፖለቲካ የተጠመዱ አባላት ይዞ የጳጳሱን የአቡኑ ቀሲሱንም ስራ እኔ ልስራ ማለት ስርዓተ ቤተክርስትያን መጠበቅን አያመለክትም ፡፡ 
  • ……አስተማርናቸው ያሏቸውን ምናልባትም ባለሰንሰለቱ ሳይሆን ታጣፊውን ታንክ እስከ ትከሻቸው እስከመያዝ ይታመኑናል ብለው የሚያስቧቸውን ለአደጋ አጋልጠው ቤተክርስትያን ሊያደኽይዋት ይችላሉ፡፡ 
  • መናፍቃንን በመለፍለፍ ወይም በስለላ እና በዱላ ማሸነፍ አይቻልም፡፡ ያውም እነሱ ጫማ ስር ተደፍቶ፡፡ የቃለ እግዚሐብሔርን እቃ ጦር ለብሶ የመንፈስ ቅዱስን ሰይፍ ታጥቆ በቀናች በተዋህዶ ሐይማኖት ፀንቶ በምሳሌነት በመቆም እንጂ 



(ከአምደ ሃይማኖት)

‹‹ቤተክርስትያኒቷ ትዘጋ›› የሚል ሰላማዊ ሰልፍ ተካሄደ

‹‹የገሀነም ደጆች አይችሏትም››

ጊዜው ወርሀ ክረምት ነው :: የእናታችን የቅድስት ድንግል ማርያም ፆመ ፍልሰታ ወቅት ሲሆን በቤተክርስትያናችን ህግና ስርዓት መሰረት ይህ ጊዜ ዲያቆናት ፤ ካህናት መነኮሳት ፤ ጳጳሳት እና ምእመናን ለሐዋርያት የተገለፅሽላቸው እናታችን ለእኛም በምህረት አትለይን እያሉ በፆም ፤ በፀሎት ፤ በስግደት የሚለምኑበት ጊዜ ነው፡፡

ቦታው በሐረር መንገድ አዋሽ ሰባትን አልፈው ካለው የጉምሩክ የፍተሻ ጣቢያ ትንሽ ኪሎ ሜትር አለፍ ብሎ ከአሰቦት ገዳም መገንጠያ ሳይደርስ ከዋናው አስፋልት አንድ ኪሎ ሜትር ላይ የሚገኝ የአባታችን የአቡነ ገብረመንፈስ ቅዱስ ቤተክርስትያን ሲሆን የቦታው ስም ቦርደዴ በመባል ይታወቃል፡፡ ይህ ቤተክርስትያን የሚገኝበት ቦታ ላይ ከ30 የማይበልጡ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ አማኞች ሲገኙ በቁጥር ከ40 እና ከ50 እጥፍ ልቀው የሚገኙት ግን ሙስሊም ማህበረሰቦች ናቸው፡፡ ይህ ቦታ ለአንድ አፍታም ቢሆን ከነገር እና ከትንኮሳ እፎይ ያለበት ጊዜ የለም፡፡ ቦታ ድረስ ሄጄ በተመለከትኩበት ጊዜ እዚህ ቦታ ላይ ያለው የሙቀት መጠን ክረምት ሳይል በጋ ከ40 ድግሪ በላይ ስለሆነ ቆሞ ማስቀደስ እንደ እግዚሐብሔር መልካም ፍቃድ ፤ ምህረት ፤ ቸርነት እንጂ እንደ እኛ ብርታትና ጥንካሬ እንዳልሆነ ተረድቻለሁ፡፡
ቤተክርስትያኒቷ አካባቢ ያሉት ምዕመና ጧፍ ፤ እጣን ፤ ዘቢብ እና ንዋየ ቅዱሳትን ማሟላት አቅሙ ስለሌላቸው ይህ ችግር የቀን ተቀን የውስጥ ችግር ችግራቸው ሆኖ አሁንም አሉ ፡፡ የባሰ አታም ነውና  አንድ ጊዜ ቅዳሴ ላይ ወንጌል ለማንበብ ጧፍ አልቆ በኩራዝ የተጠቀሙበት ጊዜም ነበር ፡፡
በአካባቢው የሚገኙ ከአክራሪ ወገን የሚመደቡት የእስልምና ተከታዮች በአካባቢው ላይ ለ24 ሰዓት ያህል ከ4 በሚበልጡ መስኪዶቻቸውን ድምፅ ማውጫ Speaker ወደ ቤተክርስትያን አዙረው ‹‹አላህ ዋክበር›› በሚሉበት ሁኔታ ላይ ምንም ጥያቄ ያላቀረቡት በአካባቢው የሚገኙ  ክርስትያኖች በዓመት አንድ ጊዜ ለ16 ቀናት ብቻ ያለውን የሱባኤ ጊዜ ለሊት ሰዓታት እና ኪዳኑ ፤ ጠዋት ትርጓሜው እና ስብከቱ ፤ ከሰዓት ቅዳሴው ረበሸን ብለው ቤተክርስትያኒቷ እንድትዘጋላቸው  ለአካባቢያቸው ወረዳ አስተዳደር ሰላማዊ ሰልፍ አድርገው መጠየቃቸውን አረጋግጠናል፡፡ ይህን ጥያቄ የመስተዳድሩ  ሃላፊ ከሰማ በኋላ ለሚቀጥለው ቀን የቀጠራቸው ሲሆን በሚቀጥለው ቀን ሲመጡ ምንም ምላሽ ስላላገኙ ሓላፊውን በኃይል ከቢሮ ያባረሩት ሲሆን ፡፡ ይህ ጥያቄያቸው የክልሉ መንግስ ጋር እንደደረሰ ፤ አካባቢው ላይ የሚገኙ ክርስትያኖች ጉዳዩን ወደ ፊደራል መንግስት የወሰዱት ሲሆን መንግስት የዛኑ ቀን ማታ አካባቢው ላይ የሚገኙ ፌደራል ፖሊሶች ማታ 3፡00 አካባቢ ወደ አካባቢው በፓትሮል በመምጣት ይህን ጥያቄ የጠየቁትን ሰዎች ግማሽ ያህሉን ለቅመው ወስደው ወደ እስር ቤት የከተቷቸው  ሲሆን የተቀሩትን ግን ሸሽተው አምልጠዋል፡፡ መንግስት ይህን እርምጃ ከወሰደ በኋላ ሁኔታውን በጥቂቱ ያረጋጋ ሲሆን ፡፡ በአሁኑ ወቅት አካባቢው በፊደራል ፖሊስ  እየተጠበቀ ይገኛል::

እኛ በአሁኑ ሰዓት እንትና 18 ገፅ ወቀሳ ፃፈ ፤ ያኛው ሰባኪ አውደ ምህረት ላይ እንዳይቆም ተከለከለ ፤ በዚህ መፅሄት ላይ እንትና መልስ ሰጠ ፤ አንዱ ይቅርታ አለ ሌላኛው ይቅርታ ተቀበለ እያልን ስራ መስራት በሚገባን ወቅት ወሬ ስናራግብ ለቤተክርስትያን መሆን በሚገባን ሰዓት ጊዜያችንን እና አቅማችንን አልባሌ ቦታ ላይ በማዋልና ትርፍ የሌለው ስራ በመስት ላይ እንገኛለን፡፡

አሁንም ጊዜው አልረፈደም ስለ ጥቂት ሰዎች ማውራታችንን አቁመን ስለ ቅድስት ቤተክርስትያን ዘብ እንቁም ዛሬ በሰላማዊ ሰልፍ ይህን የጠየቁ ሰዎች ነገ ምን ማድረግ እንደሚያስቡ ለማስረዳት መምህር ሊያሻን አይገባም፡፡

በዚች ምድር ላይ የምንቆየው እንደ ማቱሳላ 969 ዓመት አለመሆኑን አውቀን በኖርንበት፤በምንኖርበት  ጊዜ ሁሉ ከቤተክርስትያን ጎን ለመቆም ያብቃል፡፡

(ከአምደ ሃይማኖት)

ሐሰት አንናገርም፤ እውነትንም አንደብቅም
‹እግዚሐብሔር ቤተክርስትያንን ይጠብቅ ››

Friday, August 26, 2011

ዲያቆን ዳን ኤል ክብረት የዓለም የሰላም አምባሳደ ተብሎ በፕሬዘዳንት ግርማ ተሸለመ

(ምንጭ፡-አዲስ ዘመን ነሐሴ 12 ቀን 2003ዓ.ም. 70ኛ ዓመት ቁጥር 342)

ቪዥን ኢትዮጵያ ፎረ ዲሞክራሲ የተባለ መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት መልካም ዜጋን በመቅረጽ እና የመልካም አስተዳደር ተግባራትን በማጠናከር ረገድ ከፍተኛ አስተዋጽኦ አድርገዋል ያላቸውን አራት ግለሰቦች ሊቀ ዲሞክራት እና ስድስት ግለሰቦችን ‘’የዓለም የሰላም አምባሳደር’’ የሚል ማዕረግ ሰጥቷል፣ በዚህም የነገረ ቤተክርስቲያን ተመራማሪ እና ደራሲ የሆነው ዲ/ን ዳንኤል ክብረት ‘’የዓለም የሰላም አምባሳደር’’ የሚል ማዕረግ ሰጥቶቷል፡፡


 
ስነስርዐቱ ላይ በመገኘት ማዕረጉን የሰጡት ፕሬዚዳንት ግርማ ወልደጊዮርጊስ ሲሆኑ የፌደራል ጉዳዮች ሚንስትር ዶ/ር ሽፈራው ተክለማርያም ‘’የዓለም የሰላም አምባሳደር’’ የሚል ማዕረግ ካገኙት ግለሰቦች አንዱ ናቸው፡፡ ቪዥን ኢትዮጵያ ፎረ ዲሞክራሲ ዋና ዳይሬክተር አቶ ታደለ ደርሰህ በስነስርዐቱ ላይ እንደገለጹት የተመረጡት ግለሰቦች በግልና በመንግስታዊ ተቋማት የላቀ ሥራ የሰሩ ናቸው፡፡ የዜጎች መብት እንዲታወቅ ና እንዲከበር ከፍ ያሉ ተግባራት አከናውነዋል አርአያና ምሳሌ ሆነው የሚጠቀሱም ናቸው ድርጅታችን ወደፊትም እንዲህ ያሉ ግለሰቦችንና ኃላፊዎችን ለተግባራቸው ዕውቅና በመስጠት የመሸለም ሥራ እንደሚሰራ ገልጸዋል፡፡ ለአገልግሎት ባሕር ማዶ የሚገኘው ዲ/ን ዳንኤል ክብረትም በባለቤቱ አማካኝነት የማዕረግ ስጦታውን ተቀብሏል

የአቡነ አብርሃምና አቡነ ኤውስጣጤዎስ ጉዳይ

የኢትዮጲያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያንን ወክለው በውጭ ገር ያሉ ሊቃነ ጳጳሳት ለጥቅምቱ የቅዱስ ሲኖዶስ ጉባኤ ወደ ገር ቤት እንዲመጡ የማስጠንቀቂያ ደብዳቤ እንደተላከላቸው ታውል።

በዓመት ሁለት ጊዜ የሚደረገው የቅዱስ ሲኖዶስ ጉባኤ ላይ በሀገር ውስጥ እና በውጭ ቤተ ክርስቲያንን ወክለው ሀገረስብከት የሚያሰተዳድሩ ሊቃነ ጳጳሳት ከአቅም በላይ ካልሆነ በስተቀር በአካል መገኘት አለባቸው።ነገር ግን የተወሰኑት ሊቃነ ጳጳሳት ባልታወቀ ምክንያት ባለፉት አራት እና አምስት ዓመታት በጉባኤው ያልተገኙ መሆኑ ግራ የሚያጋባ ጉዳይ ሆኖአል። በተለይም በአሜሪካን ገር ያሉት ብፁዕ አቡነ አብረሃም እና አቡነ ኤዎስጣቲዎስ እንዲሁም በሰሜን ምዕራብ አውሮፓ የሚገኙት ብፁዕ አቡነ እንጦንስ አዲስ አበባ በሚደረገው ርክበ ካህናት ጉባኤ ከተሳተፉ አምስተኛ ዓመታቸው ሲሆን ግንኙነታቸው በስልክ እና በፋክስ ቢቻ መሆኑን ያገኘነው መረጃ ይጠቁማል።

ወደ ገር ቤት ለመሄድ ያለመፈለጋቸው ጉዳይ እቀየራለሁ ከሚል ስጋት እንደሆነ ብዙዎች ይስማማሉ ባለፈው ዓመት አቡነ አብረሃም በሌሉበት ከቦታቸው እንዲነሱ ሲወሰን በሰሜን አሜሪካ ያሉ ምዕመናን ባሰሙት ተቃውሞ እንዲቀጥሉ መደረጉ ይታወሳል።

ይህ በእንዲህ እንዳለ ለጥቅምት 2004 ዓ፡ም የቅዱስ ሲኖዶስ ጉባኤ ሁሉም ከያሉበት እንዲመጡ ትዕዛዝ የተላለፈ ሲሆን በተለይም ከላይ ለተጠቀሱ አባቶች ጥብቅ ማሳሰቢያ እንደደረሳቸው ለማወቅ ችለናል::አባቶችም የቤተ ክርስቲያንን ጉዳይ ባንድነት ለመምከር እንደሚመጡ ይጠበቃል።

(ሰበር ዜና) አቡነ አብርሃምና አቡነ ኤውስጣቴዎስ ወደ ኢትዮጵያ እንዲመለሱ ተጠየቁ

መኖሪያቸውን አሜሪካ ያደረጉ አባቶች የአቡነ አብርሃም እና የአቡነ ኤዎስጣቴዎስ ከቦታቸው መነሳት ዋነኛ አጀንዳ ነው።

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ቋሚ ሲኖዶስ መደበኛ ስብሰባ በዛሬው ዕለት ረቡዕ ነሐሴ 18 ቀን 2003 ዓ.ም ከሰዓት በኋላ እንደሚያካሂድ ተገለጸ፡፡ ከስብሰባውም አጀንዳዎች ዋነኛው በዋሽንግተን እና አካባቢው ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ አብርሃም እና የሎስ አንጀለስ ና አካባቢው ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ኤዎስጣቴዎስን ጉዳይ ይሆናል፡፡ ከቅርብ ጊዜ በፊት በቀንደኛ የተሐድሶ አራማጅነታቸው የሚታወቁትን ሊቀ ስዩማን ኃይለጊዮርጊስ “የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን የሰሜን አሜሪካ ልዩ ሹም” በማለት በቅዱስ ፓትርያሪኩ መሾማቸው ሲሆን ውሳኔውን እና ሹመቱን በመቃወም ሁለቱም ሊቃነ ጳጳሳት የተቃውሞ ድብዳቤ መጻፋቸው ነው፡፡ የተቃውሞው ይዘት ቃለ አዋዲው እና ቀኖና ቤተክርስቲያን ተጥሷል የሚል ሲሆን በአንድ ሀገረ ስብከት የሁሉም የበላይ ሊቀ ጳጳሱ መሆን ሲገባው ከሊቀ ጳጳሱ በላይ “ልዩ ሹም” መሾም ተገቢ አይደለም ይላሉ፡፡ በዚህ ተቃውሞም የተነሳ ዛሬ በሚደረገው የቋሚ ሲኖዶስ አስቸኳይ ስብሰባ ሁለቱንም ሊቃነ ጳጳሳት ከቦታቸው በማንሳት ወደ አገር ቤት አንዲሄዱ ሊወሰን እንደሚችል ቤተ ክርስቲያኒቱ ገለጸች።

ማህበረ ቅዱሳንና አቡነ ጳውሎስ በመስማማት ላይ ናቸው


የተሐድሶ መናፍቃን እንቅስቃሴን አስመልክቶ ቅዱስ ፓትርያሪኩ ከማኅበረ ቅዱሳን አመራር ጋር ውይይት አደረጉ አትም ኢሜይል

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ጳውሎስ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢተዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት የዓለም አብያተ ክርስቲያናት ምክር ቤት ፕሬዚዳንት የዓለም ሃይማኖቶች ለሰላም የክብር ፕሬዚዳንት ከማኅበረ ቅድሳን ሥራ አመራርና አስፈጻሚ ጉባኤያት ተወካዮች ጋር ነሐሴ 15 ቀን 2003 ዓ.ም ስለ ማኅበሩ አገልግሎትና በተለይም የተሐድሶ መናፍቃንን እንቅስቃሴ አስመልክቶ ውይይት ማድረጋቸውን የማኅበሩ ጽ/ቤት አስታወቀ፡፡

በቅዱስ ፓትርያሪኩ ጽ/ቤት በተካሔደው ውይይት፤ የማኅበሩ አመራር ስለተሐድሶ መናፍቃን እንቅቃሴ አራማጆችና ተቋማት የተዘጋጁ ልዩ ልዩ መጻሕፍት እንዲሁም በምስል ወድምጽ /VCD/ የታገዘ ገለጻና ማብራሪያ ቀርቧል፡፡

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ጳውሎስም በቤተ ክርስቲያኒቱ ላይ እየተፈጸመ ያለውን ድርጊት ከተመለከቱ በኋላ “ይህ ሁሉ የንብ ሠራዊት እያለ ወረራው ሲካሔድ የት ነበራችሁ?” የሚል የአባትነት ጥያቄያቸውን አቅርበዋል፡፡

ቅዱስነታቸው፤ ቤተ ክርስቲያንን እና ምእመናንን ከእንዲህ ዓይነቱ ተግባር መጠበቅ የሁሉም ሓላፊነት እንደሆነ ጠቅሰው፤ ከዚህም በላይ መብታችንን በሕግ ሳይቀር ማስከበር እንደሚኖርብን ገልጸዋል፡፡ ማኅበረ ቅዱሳን በልጅነት ደረሻው እያከናወነ ያለው አገልግሎት እንደተጠበቀ ሆኖ፤ የግለሰቦችን ስም እየጠቀሰ “ተሐድሶ ናቸው” ማለት ግን አግባብ እንዳልሆነና ይህም የቤተ ክርስቲያናችንን አሠራር ጠብቆ መፈጸም እንዳለበት አሳስበዋል፡፡

የማኅበሩ አመራር አባላትም፤ በአሁኑ ወቅት እየተከናወነ ያለው ሥራ የተሐድሶ መናፍቃን እንቅስቃሴ ምንነት፣ በእንዴት ዓይነት ሁኔታና ደረጃ ላይ እንደሚገኝ ምእመናን ግንዛቤ አግኝተው ራሳቸውን እንዲጠብቁ፤ እንዲሁም ፕሮቴስታንታዊ የተሐድሶ መናፍቃን እንቅስቃሴን የሚመሩና የሚደግፉ ተቋማትን፣ ስልትና አሠራራቸውን የማሳወቅ ሥራ እንደሆነ ገልጸዋል፡፡

ማኅበረ ቅዱሳን በ1990 ዓ.ም የተሐድሶ መናፍቃንን እንቅስቃሴ የማጋለጥ ሰፊ ሥራ ባከናወነበት ወቅት፤ በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ሆነው ነገር ግን ፕሮቴስታንታዊ የተሐድሶ ኑፋቄ በምእመኑ ውስጥ በመዝራት ጉልህ ድርሻ የነበራቸው “መነኮሳት” ተወግዘው እንዲለዩ ሲደረግ፤ በቤተ ክርስቲያን ሥርዐትና አሠራር መሠረት ማኅበሩ አስፈላጊውን መረጃና ማስረጃ ለሊቃውንት ጉባኤ አቅርቦ ከዚያም በኋላ በቅዱስ ሲኖዶስ የመጨረሻ ውሳኔ እንዲሰጥ ያደረገበት ሁኔታ እንደነበረ፤ የማኅበሩ አመራር አባላት በውይይቱ ላይ አስታውሰው፤ ማኅበሩ የቅድስት ቤተ ክርስቲያንን ሥርዐትና አሠራር ጠንቅቆ እንደሚያውቅና ይህንኑ ለማስጠበቅ ጠንክሮ እንደሚሠራ ገልጸዋል፡፡ አሁንም ማኅበረ ቅዱሳን እየሠራ ያለው የግለሰቦችን ስም በመጥቀስ “ተሐድሶ” የማለት ሳይሆን፤ ስለ ተሐድሶ መናፍቃን እንቅስቃሴ ምንነትና ስልት ግንዛቤ እንዲኖር በማድረግ ምእመናን ራሳቸውን እንዲጠብቁ የማሳወቅ ሥራ እየተከናወነ እንደሆነ ማብራሪያ ተሰጥቷል፡፡
ወደፊትም በዚህ የተሐድሶ መናፍቃን እንቅስቃሴና ሥራ ላይ የተጠመዱ ነገር ግን በቤተ ክርስቲያኒቷ ውስጥ የሚገኙ አካላትንና ደጋፊዎችን፤ የቅድስት ቤተ ክርስቲያንን ሥርዐትና አሠራር በመጠበቅ ማኅበረ ቅዱሳን ለሚመለከታቸው የቤተ ክርስቲያን አካላትና አባቶች እንደሚያቀርብ በማኅበሩ አመራር አባላት ለቅዱስነታቸው ተገልጿል፡፡

ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያሪኩም፤ በበቂ መረጃ በማስደገፍ ለሚመለከተው የቤተ ክርስቲያን አካል በማቅረብ ሁሉም ነገር በሕግና በሥርዐት መከናወን እንዳለበት አባታዊ መመሪያ ሰጥተዋል፡፡

ስለ ተሐድሶ ፕሮቴስታንታዊ ጉዳይ በሊቀ ትጉሃን ዘሪሁን ሙላቱ ሰላም የሰጠው ቃለ ምልልስ

ስለ ተሐድሶ ፕሮቴስታንታዊ እንቅስቃሴዎችን በተመለከተ ሊቀ ትጉሃን ዘሪሁን ያስተላለፈውን መልዕክት እነሆ!!! ምንጭ (ደጀ ሰላም)

ስለ ተሐድሶ እና ተያያዥ ጉዳዮች የዘሪሁን ሙላቱ ቃለ ምልልስ


“የሃይማኖታችን ጉዳይ የፓትርያርኩ ብቻ አይደለም” የሚለው ሊቀ ትጉሃን ዘሪሁን ሙላቱ ከቅ/ሥላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ  የመጀመሪያ ዲግሪውን በሥነ መለኮት፣ ሁለተኛ ዲግሪውን ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በድኅረ ምረቃ መርሐ ግብር በፊሎሎጂ ትምህርት ተመርቋል። በአሁኑ ወቅትም ደግሞ የዶክትሬት (ፒ.ኤች.ዲ) ጥናቱን በማገባደድ ላይ ነው። በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ላይ ተሐድሶ እንቅስቃሴ ወቅታዊ ሁኔታ እና ቤተ ክርስቲያኒቱ በምትከተለው አስተምህሮ ዙሪያ ከዕንቁ መጽሔት ጋር ያደረገው ቃለ ምልልስ እንደሚከተለው ቀርቧል።
 
 
ከዚህ በታች ያለውን ሙሉ ቃለ መጠይቁን እንድታነቡ በአክብሮት እንጠይቃለን!!!

ብፁእ አቡነ ሚካኤል አረፉ

ስለ "ብፁዕ አቡነ ሚካኤል" የማ/ቅዱሳን ዘገባ

(Mahibere Kidusan):- የሰሜን ምዕራብ ትግራይ ሽሬ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስና የቅዱስ ሲኖዶስ አባል ብፁዕ አቡነ ሚካኤል ነሐሴ 8 ቀን 2003 ዓ.ም አርፈዋል። በአንብሮተ ዕድ ከተሾሙበት ከነሐሴ 22 ቀን 1997 ዓ.ም ጀምሮ በአሁኑ ሀገረ ስብከታቸው የተሾሙ ሲሆን በመካከል ለተወሰኑ ወራት የወላይታ፣ ዳውሮና ኮንታ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ሆነው አገልግለዋል።

የሐሞት ጠጠር ሕመም የነበረባቸው ብፁዕነታቸው የቀዶ ጥገና ሕክምናቸውን በቅዱስ ገብርኤል ሆስፒታል በመከታተል ላይ የነበሩ ሲሆን በመካከል ከሰመመናቸው መንቃት ሳይችሉ እንደቀሩ ምንጮቻችን ገልጸዋል። ቀጣይ የአስከሬን ምርመራ ከተደረገ በኋላ ምክንያቱ ሊገለጽ እንደሚችልም ይገመታል።

በቅዱስ ሲኖዶስ ምርጫ በትግራይ ክልል ሰሜናዊ ምዕራብ ዞን የተሾሙት የቀድሞው ሊቀ ሥልጣናት አባ ተክለ ሚካኤል ዓባይ አሁን ብፁዕ አቡነ ሚካኤል በቀድሞው አድዋ አውራጃ በዓምባ ሰነይቲ ወረዳ በላውሳ ቅዱስ ገብርኤል አካባቢ ከአለቃ ዓባይ ወ/ገብርኤልና ከወ/ሮ ታደለች ንጉሤ በ1942 ዓ.ም ተወለዱ፡፡

በታላቁ በደብረ ዓባይ ገዳም ከመምህር አበራና ከመምህር ገብረ እግዚአብሔር ከመሠረተ ትምህርት እስከ ጸዋትወ ዜማ፣ ከመምህር የኔታ የኋላእሸት መዝገበ ቅዳሴ ጠንቅቀው ከተማሩ በኋላ በመምህርነት ተመርቀዋል፡፡

በዋልድባ ገዳም መዓርገ ምንኩስና ተቀብለዋል፡፡ ጎንደር ክፍለ ሀገር በወገራ አውራጃ በጉንተር አቦ ከመሪጌታ ሐረገወይን፣ ጎንደር ከተማ ከመምህር እፁብ ቅኔ ተምረው ተቀኝተዋል፡፡

በሐረርጌ ክፍለ ሀገር ቁልቢ ቅዱስ ገብርኤል ገዳም እያገለገሉ የአንደኛና መለስተኛ ሁለተኛ ደረጃ ዘመናዊ ትምህርታቸውን ተከታትለዋል፡፡ በሰዋስወ ብርሃን ቅዱስ ጳውሎስ ት/ቤት በአዳሪነት ገብተው የሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን አጠናቀዋል፡፡

በውጪ አገር እንግሊዝ ለንደን ሴንት ኤድዋርድስ ኮሌጅ የመጽሐፍ ቅዱስ ኮርስና የእንግሊዝኛ ቋንቋ ለአንድ ዓመት፣ ግሪክ አገር በአቴንስ ዩኒቨርስቲ ለስድስት ዓመታት ከፍተኛ መንፈሳዊ ትምህርት በመማር በቲኦሎጂ ማስትሬት ዲግሪ፣ በአሜሪካ ሆሊ ክሮስ በተባለው የግሪክ ሴሚናሪ ከሲስተማቲክ ቲኦሎጂ ዲፕሎማ፣ በቦስተን ዩኒቨርስቲ የኤስ.ቲኤም ወይም በፓስተራል ካውንስሊንግ /ሳይኮሎጂ/ በማስተርስ ዲግሪ ተመርቀዋል፡፡

በተለያዩ ጊዜያት በጠቅላይ ቤተ ክህነት የእስኮላር ሽፕ ዋና ክፍል ኃላፊ፣ የኢትዮጵያ ገዳማት መምሪያ ኃላፊ፣ የቅዱስ ጳውሎስ ከፍተኛ መንፈሳዊ ት/ቤት ዲን፣ በወቅቱ የኤርትራ ሀገረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣ የዕቅድና ጥናት መምሪያ ኃላፊ፣ የትንሣኤ ዘጉባኤ ማተሚያ ቤት የበላይ ኃላፊ፣ የቅድስት ሥላሴ ካቴድራል አስተዳዳሪ፣ በጠቅላይ ቤተ ክህነት የካህናት አስተዳደር መምሪያ ኃላፊ፣ የትምህርትና ሥልጠና መምሪያ ሐላፊ በመሆን አገልግለዋል፡፡

የብፁዕነታቸው የቀብር ሥነሥርዓት ዛሬ ነሐሴ 10 ቀን 2003 ዓ.ም ከዘጠኝ ሰዓት ጀምሮ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ጳውሎስ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ፣ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳትና እንግዶች እንዲሁም ምእመናን በተገኙበት በቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ይፈጸማል።